የመነሻ ሀሳብ

ስሜ ማለት በውስጣችን ወይም በውጭ ለሚከሰቱ ሁኔታዎች ሁሉ ስለሁኔታዎች ባለን አመለካከት መሠረት የሚኖረን አመሯዊ ሁኔታ ወይም ምላሽ ነው፡፡ ስሜታችን በማንኛውም ጊዜ ከእኛ ጋር ነው፡፡ በህይወት እስካለን ድረስ ከስሜት ውጭ የምንሆንበት አንዳችም ቅጽበት የለም፡፡ ስሜት የእያንዳንዳችን ህይወት መገንባት ወይም ፍረስ ና የሚጫወት የህይወታችን የመሰረት ድጋይ ነው:: 

በማንኛውም የህይወታችን ቅፅበት ውሳኔዎችን እንድንወስን እና በወሰነውም መሠረት እንድንሰራ በማድረግ የስራችንን አጸፋ ውጤት እንድናገኝ የሚያስችለን ስሜት ነው። ስለሆነም ሰው በማንኛውም ቅጽበት ለውስጣዊ እና ውጫዊ ሁኔታዎች ያለውን የራሱን ስሜት የመቆጣጠር ክህሎት በህይወታችን ለቅጽበት ችላ የማይለው ቁልፍ ጉዳይ ነው፡፡

ነገር ግን ብዙ ሰው እርሱ ከስሜቱ በላይ፣ ሁሉም ስሜቶቹ በእርሱ ቁጥጥሩ አንደሆኑ እና ስሜቶቹን እንዴት መቆጣጠር እንዳለበት አያውቅም፡፡ ስለሆነም እኔኮ እንደዚህ ነኝ፣ እኔኮ እንደዛ ነኝ ... እያለ ስሜቶቹን እንደ ማንነት መገለጫው እና እንደማይቆጣጠራቸው የህይወት እጣፍንታው አድርጎ ይወስዳቸዋል:: ከዚህም የተነሳ እነዚያ ስሜቶች ማለትም መናደድ፣ ማፈር፣ ማዘን ... ወዘተ በህይወቱ እያሰቃዩት እና ከሰዎች እያጋጩት ይኖራል::

ስሜታችንን የመቆጣጠር ክህሎት ከሌለን ውሳኒያችን፣ እርምጃችን እና ውጤታችን ብሎም ህይወታችን ምን ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ቀላል ነው፡፡ ለእያንዳንዷ የአፍታ ቅጽበታዊ ሁኔታ ስሜታችንን መቆጣጠር ባለመቻላችን ህይወታችንን የተሳሳቱ ውሳኔዎች በመወሰን እና የተሳሳቱ እርምጃዎች በመውሰድ ያልተፈለጉ ውጤቶችን እያጨድን ጸጸት የተሞላበት ህይወት እንኖራለን

ለዚህም ነው ሰው በህይወቱ ማሰብ እና ማተኮር ያለበት ትልቁ ጉዳዩ ምን እንደደረሰበት ማሰብ ሳይሆን በህይወቱ ለደረሰበት ምን ምላሽ መስጠት እንደለበት ማሰብ ነው የሚባለው፡፡ ምክንያቱም በህይወቱ ስለሚደርስበት ነገር አሰበም አላሰበም ይደርስበታል፡፡ ስለሚሰጠው ምላሽ ግን አእምሮውን ተጠቅሞ ማሰብ ስሜቱን በመቆጣጠር ለክስተቱ የሚሰጠውን ምላሽ ራሱ መወሰን ይችላልና::

ስሜቶቻችን ሙሉ በሙሉ በእራሳችን ቁጥጥር ስር ፡፡ እንዲያውም ስሜቶቻችን በአግባቡ እና በብልሃት ከተጠቀምንባቸው እንደ ህይወት አማካሪያችን ሆነው ያገለግላሉም፡፡

በዙሪያችን ያለው ሁኔታ ምንም ይሁን ምን ለምሳሌ እንደ ፍቅር ወይም ጥላቻ፣ ደስታ ወይም ሀዘን፣ ጥሩ ወይም መጥፎ፣ ጤና ወይም ህመም፣ ስኬት ወይም ውድቀት ብቻ የፈለገነውን ስሜት መላበስ እና ማንጸባረቅ እንችላለን ወሳ ጥያቄ ግን የትኛውን ስሜት ብንላበስ እና ብናንጸባርቅ ይሻለናል ነው፡፡ አዎንታዊውን ወይስ አሉታዊውን፣ ገንቢውን ወይስ አፍራሹን

ሁላችን አዎንታዊውን እና ገንቢውን እንደምንል አልጠራጠርም፡፡ አው፣ ሁኔታው ምንም ይሁን ምን አዎንታዊውን እና ገንቢውን ስሜት መላበስ እና ንጸባርቅ ይሻለናል እንችላለን፡፡ 

ልብ ካልክ አንተ ማለት ከስሜቶችህ እጅግ በጣም ከፍ ያልክ እና የራስህን ስሜት መቆጣጠር የምትችል እና የማይናወጥ መሰረት ያለህ ሰው መሆንህን በሀይወትህ መመስከር እና መግለጽ ትችላለህ። 

ስሜት ህይወታችን ውስጥ እንዴት እንደሚሰራ እና ምን ያህል በራሳችን ቁጥጥር ስር እንደሆነ በተረዳንበት ቅጽበት፣ በእኛ ላይ ለሚከሰቱ ውጫዊ ክስተቶች ያለን አመለካከት እና ምላሽ ሁሌም አዎንታ እና ገንቢ ይሆናል በእኛ ላይ የሚከሰት እያንዳንዱ ውጫዊ ሁኔታ ወይም ክስተት ሙሉ በሙሉ በራሳችን ቁጥጥር ውስጥ ባሉ ስሜቶች መልክ የሚከሰት የአዕምሮ ጨዋታ መሆኑንም  እንገነዘባለን፡፡ 

ከዚህም ጋር ተያይዞ በህይወታችን በሚከሰቱ ማናቸውም ክስተቶች በእኛ ላይ የሚያስከትለት ውጤት በእኛው ቁጥጥር ስር ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህንን እውነታ በተረዳን ጊዜ እና በራሳችን የዕለት ተዕለት ህይወት ውስጥ ልምምድ በምናደርግበት ጊዜ፣ ምንም ነገር ከመሆን፣ ከማግኘት እና የፈለግነውን ከማድረግ የሚያግን አንዳች ነገር እንደሌለ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ይሆንልናል።  ብሎም ምንም ዓይነት ተግዳሮት ስኬታማ  ከመሆን እንደማያግደን እንገነዘባለን፡፡

በአጠቃላይ በማንኛውንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሆነን የፈለግነውን ስሜት መላበስ እና ንጸባርቅ እንላለን፡፡ በመሆኑም የምንፈልገውን ስሜ መላበስ እና ንጸባርቅ ምንም አይነት ሁኔታ አይገድበንም፡፡ 

ስሜቴቻችንን የመቆጣጠር እና ማስተዳደር ክህሎት ሲኖረን ማንም ሰው እና ምንም ዓይነት ሁኔታ በምንም መንገድ እኛን ዝቅ ማድረግም አይችልም፡፡ ራሳችን እያወቅን በንቁ አዕምሯቸን ወይም ሳናውቅ በድብቁ አዕምሯቸን ካልፈቀድንለት እና የዝቅተኝነት ስሜትን ካልተላበስን እና ካላንጸባረቅን በስተቀር፡፡ እግዚአብሔር በነፃ ከተሰጡን የሰው ልጅ ስጦታዎቸ መካከል በማንኛውም ሁኔታ የምንፈልገውን ስሜት የመላበስ እና የማንጸባረቅ ችሎታ አንዱ ነው፡፡ 

ለዚህም በማንውም ሀይወት ሁኔታ ውስ ሆነህ የሚጠቅምህን ስሜት የመላበስ እና የማንጸባረቅ ልማድ በተደጋጋሚ ሆነ ብለህ በመለማመድ ገንዘብህ ማድረግ አለብህ፡፡ ይህንን ደረክ እንደሆን በምንም ዓይነት ፈተና ውስጥ ሆነህ እንኳን ሳይቀር ነገሮችን በስኬት የምከውንበት መንገድ ይታይሃል፡፡ 

ከዚህም በኋላ ራስህን በስሜትህ አሳንሰህ መግለጽ የለብህም እኔ ተናዳጅ ነኝ፣ እኔ አይናአፋር ነኝ እኔ ... ወዘተ ብሎ ነገር የለም፣ ማለት የለብህም፡፡ ይልቁንም አንተ ከእነዚህ ሁሉ በላይ ነህና:: 

ለጥያቄዎች ምላሽ፣ ለቀረቡት ሃሳቦች ማንኛውም ሀሳብ አስተያየት ወይም ጥያቄ ካለ በዘህ ድሀረ-ገጽ ፃፉልን