መነሻ ሃሳብ

ልጅነት እጅግ በጣም ድንቅ የህይወት ክፍል ነው፡፡ ልጅነት የፈጣሪውን ማንነት የሚያነንጸባርቅ ድንቅ ማንነት ነው ማለትም መልካም፣ መጨነቅ የማያውቅ ይልቁንም ነፃና ደስተኛ፣ ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ የሚያምን፣ ምንም ተንኮል፣ ክፋት፣ ቅናት ... ወዘተ ጨምሩበት የማያውቀው ድንቅ ማንነት ነው፡፡    

ልጅነት ፈሳሽ ማንነት ነው፡፡ ፈሳሽ ልክ የመያዣ ዕቃውን ቅርጽ እደሚይዝ ሁሉ ልጅነትም በቅርቡ ሆኖ የሚያየውን ሰው ሙሉ ማንነት ይሆናል፡፡ በቅርቡ ያሉት ሰዎች ማንነት ልክ ብርጭቆ የውሃን ቅርጽ እደሚወስን ሁሉ እነሱም የልጆችን ማንነት በራሳቸው አምሳል ይቀርጹታል ማለት ነው፡፡ ይህንን እውነታ ወላጆች እና ማንኛውም ልጆችን በቅርብ ሆነው የሚያሰድጉ ሰዎች በሚገባ ሊረዱት ይገባል፡፡

ልጅነት እና ስኬት

ወደ ርዕሰ-ጉዳያችን ለመምት አንዴ ወደ ልጅነታችን ወይም ልጆች ካሉን ወደ ልጆቻችን ህይወት መለስ እንበል:: በህፃንነታችን ለመዳህ፣ ለመቆም፣ በእግራችን ለመሄድ፣ ለመሮጥ፣ ለመናገር፣ /ቤት ገብተን ፊደላትን ለመለየት፣ ለማንበብ፣ ለመፃፍ፣ ... ወዘተ ጨምሩበት ምን ያህል ጊዜ ወስዶብናል? መልሱን ሳምንታ ወራት፣ ዓመታትም ጭምር እንደምትሉ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን የህይወት ልምምዶች ለማሳካት ምን ያህል ጊዜስ ሞክረናል

መልሱን ለመቁጠር የሚያዳግት ያህል እጅግ በጣም ብዙ ጊዜ ግን ያን የፈለግነውን ነገር በአስተማማኝ ሁኔታ እስከምንችለው ድረስ እንደምትሉ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

የልጅነት ማንነትን መነጠቅ 

ታዲያ ስናድግ እና ማገናዘብ ስንጀምር ያን ድንቅ ማንነት ማለትም መልካም፣ ነፃና ደስተኛ፣ ቅን፣ ርህሩህ፣ ትሁት፣ ሃቀኛ፣ ታታሪ ምንም ደከመኝ እና ሰለቸኝ የማይለው እና ውድቀትን የማይፈራው የህፃንነታችን ለመዳህ፣ ለመቆም፣ በእግራችን ለመሄድ፣ ለመሮጥ፣ ለመናገር፣ /ቤት ገብተን ፊደላትን ለመለየት፣ ለማንበብ፣ ለመፃፍ፣ ... ወዘተ ተደጋጋሚ እና ያላሰለሰ ጥረታችንን ወዴት ጠፋብን?

የምንፈልገውን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ዓላማችን ግብ እስከሚመታ ድረስ የማንሞክር ስለምንድን ነው? ይህ ብቻም አይደለም፡፡ መልካም፣ መጨነቅ የማያውቅ ይልቁንም ነፃና ደስተኛ፣ ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ የሚያምን፣ ምንም ተንኮል፣ ክፋት፣ ቅናትወዘተ ጨምሩበት የማያውቀው የፈጣሪውን ማንነት ሙሉ በሙሉ የሚያንጸባርቀው የህፃንነት ማንነታችን ዛሬ ስናውቅ የት ሄደብን ነው ተንኮለኛ፣ ክፉ፣ ቅናተናወዘተ የሆንነውይህንንስ ማንነት ከየት መጣነው?

ብዙዎቻችን እኛ ሰዎች እያደግን ስንመጣ ባቅራቢያችን በነበሩ ሰዎች፣ በት/ቤቶች፣ በዙሪያችን እና አካባባቢያችን ባሉ ሰዎችወዘተ የተነጠቅነው ትልቁን እና እንደ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ያለውን ውብ እና ድንቅ ማንነታችን ነው፡፡ ትልቁ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ ግን ያንን የልጅነት ማንነታችን በማንሳት በናፍቆት ማሰብ እና መለያየት ሳይሆን ያንን እጅግ ውብ እና ድንቅ የህፃንነት ማንነት እንዴት ዛሬ መልሰን እናግኘው ነው እና ጽሁፉን እስከ መጨረሻው በትኩረት ያንብቡ፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ ደተፃፈው እንደህፃናት ካልሆናችሁ መንግስተ-ሰማያትን አትወርሱም የሚለው የእግዚአብሔር ቃል መሠረትም ይህ ነው፡፡ 

የልጅነት ማንነትን መልሶ ማግኘት ወይም መሆን

ዛሬስ አሁን ላይ መሆን፣ ማግኘት እና መስራት በምንፈልገው ማንውም ነገር ላይ የልጅነታችን የማወቅ፣ የመሞከር እና የመስራት ጉጉት፣ ያላሰለሰ ተደጋጋሚ ሙከራ እና ደግነት፣ አዎንታዊ አሳቢ፣ ቅንነትወዘተ ማንነት ... መልሰን ማግኘት ብችልስ?

ይህ ጥያቄ ከላይ ከላዩ ሲታይ ተራ ይመስላል፡፡ ልብ ላለው ግን እጅግ በጣም አስተማሪ እና ህወት ቀያሪ ሆኖ አግቸዋለሁ፡፡ አሁን ያንን ማንነት እንዴት መልሰን ማምጣት እንደምንችል ልንነጋገር ስለሆነ ይህንን ጽሁፍ በሙሉ ትኩረት ሆናችሁ ማንበብ ቀጥሉ፡፡

ጥልቅ የመስራት፣ የመሞከር፣ ውድቀትን እንደምንም የማይቆጥር፣ ብሳሳትስ ሰዎች ምን ይሉኝ ብሎ የማይፈራ እንዲሁም ደግ፣ ቅን፣ አዎንታዊ ብቻ አሳቢ፣ የማይጨነቅ፣ ሁሌ ደስተኛ የሆነው የህፃንነት ማንነታችን ነበር፡፡ ዛሬ ወዳለው ፍልጎት አልባ፣ ምንም ሳይሞክር የሚደክም እና በቀላሉ ተስፋ የሚቆርጥ፣ መውደቁ እርሱን ከሚጎዳው በላይ ሰዎች ምን ይሉኝ ብሎ የሚጨነቅ፣ እንዲሁም ተንኮለኛ፣ ጨለምተኛ፣ በአብዛኛው አሉታዊ አሳቢ፣ ጭንቀታም... (ጥሩ ላልሆኑ ቃላቶች ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ ብዙዎቻችንን ቢያንስ ራሴን የሚገልጽ ሆኖ ስላገኘሁት ነውየሆነን የማንፈልገው ማንነት ከየት እና እንዴት ገነባነው ወይም እንዴት አገነው?

ይህ የማንፈልገው ማንነታችን ግንባታ ከላይ እደገለጽነው መንስኤው ልምምድ ሲሆን ውጤቱ ድግሞ ልማድ ነው፡፡ ልምምድ እና ልማድ ከሰው ልጆች ህይወት ተነጥለው የማይታዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች እና ወሳኝ የህይወት መንስኤ-ውጤት ምሮች ናቸው፡፡ ስለሆነም ዛሬ ላይ የሆንነው የማንፈልገው ማንነታችን የተገነባው በቅርባችን በነበሩ ሰዎች (ወላጅ፣ አሳዳጊ፣ ተንከባካቢ) በት/ቤቶች፣ በዙሪያችን እና አካባባቢያችን በነበሩ ሰዎችበተደጋጋሚ በነገሩን፣ ባስተማሩን፣ ባሳዩን፣ ባሰሙን (ልምምድ-ልማድ) መሰረት ነው፡፡ 

ይህ የማንፈልገው ማንነታችን ባልታወቀ እና ባልታቀደ መልኩ በዚህ ደረጃ ከተገነባ በእውቀት ተመስርተን እና አቅደን የምፈልገውን አዲስ ማንነት መገንባት እንችላለን፡፡ ሂደቱም ልክ ይህ የማንፈልገው የዛሬው ማንነታችን በመጣበት መንገድ ሌላ የምንፈልገውን አዲ ማንነት መልሰን መገንባት ነው፡፡ 

በመጀመሪያ መሆን የምንፈልገውን ሌላ አዲ ማንነት በጥንቃቄ መወሰን፡፡ 

በመቀጠልም ያኔ በቅርባችን፣ በዙሪያችን፣ /ቤታችንየነበሩ ሰዎች በተደጋጋሚ በመንገር በማሳት እና በመሆን (በልምምድ እና በልማድየማንፈለገውን ማንነት እንደገነቡልን ሁሉ ዛሬ ደግሞ እኛ የምፈለገውን ሌላ አዲስ ማንነት ራሳችን ለራሳችን በተደጋጋሚ በመንገር በምናብና በማት እና በአካል በመሆን (በልምምድ እና በልማድመገንባት ብችልስ

ይህ እኛ የምፈለገውን ሌላ አዲስ ማንነት ተደጋጋሚ ልምን እና ልማድ መገንባትን ቢፈልግም ግን መገንባት በጣም ይቻላልና እናስብበት፡፡ መሆን፣ ማግኘት እና መስራት የምንፈልገው ማንኛውም ነገር (ትንሽ ወይም ትልቅ) ከልምድ እና ልማድ ሃይል በላይ የሆነ አንዳች ነገር የለምና መሆን የምንፈልገውን ሌላ አዲስ ማንነት በዝርዝር በመግለጽ የአዲስ የማንነት ግንባታውን ዛሬ አሁን እጀምር፡፡ 

ባጠቃላም ስልታዊ ማሰብን ጨምረንበት የልጆችን ሙሉ ማንነት የእኛ ማንነት ማድረግ ከቻልን በህይወታችን በፈለግነው መጠን ስኬማ መሆን እንችላለን፡፡

እኔ በበኩሌ ይህንን ጽንሰ-ሃሳብ ከተረዳሁበት ዕለት ጀምሮ በእያንዳንዷየቀን ውሎየ እና ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ ሙከራ እና ልምምዴ የልጆችን ማንነት መላበስ ሆኗል፡፡ ማለትም መሻሻል በምፈልገው ነገር ላይ ብዙ ጊዜ መሞከር፣ ነፃ መሆን፣ ራስን መሆን፣ ባለኝ ነገር መደሰት፣ ለነገሮች ያለኝን አትኩሮት እና ጉጉት መጨመር፣ በማንኛውም ሁኔታ እውነትን መናገር፣ ሰዎችን እኩል ማየት፣ ባመንኩበት ጉዳይ ላይ እስከመጨረሻው መጽናት … የእናንተን ጨምሩበት እያደረኩ ነው፡፡

እናንተስ?


አንዴ ቆም ብለህ አስብ፡--

o አሁንኑ ልትተገብረው የምትችለው ከጽሁ የተማርከው አንድ ... ሁለት ... ሶስት ... ወዘተ ሃሳብ ምንድን ነው?  

o ስላንድ ነገር ብዙ መረጃ መኖር ዕውቀት ነው፤ መረጃውን በተግባር መጠቀም ደግሞ ጥበብ ነው!

 

አስተያየት ተጨማሪ ሃሳብ እንዲሁም ጥያቄ ካላችሁ በዚሁ ድህረ-ገጽ ፃፉልን!